መረጃዎችን ወጥነት ባለው መልኩ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

ህዳር 2/2018ዓ.ም ሚዛን፣

photo 2025 11 11 13 02 01 1

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከUNFPA ጋር በመተባበር በሚዛን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሲስተም (IMIS) ላይ ከክልሉ ለተውጣጡ የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

photo 2025 11 11 13 01 24 1

በመድረኩ መክፈቻ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የፕላንና ልማት ቢሮ ምክትልና የልማት መረጃ ሥ/ሥነ ህዝብ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሰለሞን አየለ እንደገለፁት መረጃዎች ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ በመሰብሰብና በማጥናት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትና ዕድገት ማዋል እንዲሁም የተቀናጀ የመረጃ ስርዓትን በመዘርጋትና ወደመረጃ ቋት እንዲገቡና ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ በክልሉ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

photo 2025 11 11 13 01 56 1
photo 2025 11 11 12 59 50 1

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሚዛን ቅ/ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሽመልስ ማጅቶ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባለፉት 60 ዓመታት መረጃዎችን አደራጅቶ በማቅረብ በርካታ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልፀው፤ በአንድ የመረጃ ቋት የሚተዳደር የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ያለው ተቋም መሆኑን ተናግረዋል። ክልሉ ከተደራጀ ወዲህ መረጃዎችን በራሱ የመረጃ ቋት እንዲይዝ በርካታ ሥራዎች መሰራታቸውንም አክለው ተናግረዋል።

photo 2025 11 11 13 00 22 1

በመድረኩ የለማው የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሲስተም ዳታ ቤዝ የማስተዋወቅና ተያያዥ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

photo 2025 11 11 13 01 46 1

መድረኩ በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ፣ UNFPA እና በክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ በጋራ መዘጋጀቱ ተገልጿል።

photo 2025 11 11 12 51 24 1
photo 2025 11 11 12 58 22 1