በቆጠራ ቦታ ካርታ ምንነትና አስፈላጊነት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ

የካቲት 02/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

photo 2026 02 10 11 54 31

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ አስተዳደር በሚያከናውነው የቆጠራ ቦታ ካርታ አፕዴቲንግ ስራ ምንነትና አስፈላጊነት ላይ ከሁለቱ ከተማ አስተዳደር ክፍለ ከተማዎች ለተውጣጡ የፕላንና ልማት፣ የከንቲባ ጽ/ቤትና የሥራና ክህሎት ቢሮ የስራ ኃላፊዎች በቢሾፍቱ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ።

photo 2026 02 10 11 52 53

በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ የዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ክብርት ዶ/ር ሜሮን ክፈለው በሁለቱ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በየጊዜው በተካሄዱ የአስተዳደራዊ ይዘት ለውጥ ምክንያት ከዚህ ቀደም የተሠሩትን የቆጠራ ቦታ ካርታዎችን ለአሁናዊ የስታቲስቲክስ ተግባራት በሚሆን መልኩ እንደአዲስ ማካለል አስፈላጊ መሆኑን በማስረዳት፣ ስራውን ለማሳካት የየከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች ድጋፍ እና ትኩረት የሚጠይቅ በመሆኑ፣ በጉዳዩ ላይ የጋራ መረዳት እንዲፈጠር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መዘጋጀቱን ገልፀዋል።

photo 2026 02 10 11 54 27
photo 2026 02 10 11 54 30

የተቋሙ አሁናዊ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ እና የቆጠራ ካርታ ምንነትና አስፈላጊነት ላይ ገለፃ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በመድረኩ የተሳተፉት የሥራ ኃላፊዎች በቀረበላቸው ገለፃ ስለተቋሙ አሁናዊ የሥራ እንቅስቃሴ በቂ ግንዛቤ እንዳገኙ እና በየከተማቸው ለሚካሄደው የቆጠራ ቦታ ካርታ አፕዴቲንግ ሥራ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።

photo 2026 02 10 11 52 47
photo 2026 02 10 11 52 46
photo 2026 02 10 11 52 35