የሪከርድ ስራ አመራርና የመዛግብት አስተዳደር ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

photo 2026 03 09 14 11 08

የካቲት 27/2018 ዓ.ም አዳማ፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በሪከርድና ማህደር ስራ አመራርን የመዛግብት አስተዳደር ለማዘመን የሚያስችል ስልጠና ከዋናው መስሪያ ቤትና ከ26ቱ ቅርንጭፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል።

photo 2026 03 09 14 11 09


የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ የሰው ሀብት አስተዳደር ስራ አስፈፃሚ አቶ አወል አባመጫ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሪፎርም የሰው ሀይል አቅም ግንባታ አንዱ ግብ መሆኑን አንስተው የሪከርድና ማህደር በዘመናዊ መልኩ ለማከናወን ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልፀዋል። ስራ አስፈፃሚው አክለውም የስልጠናውን አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የስልጠናው ተሳታፊዎች ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለስራው የሚያስፈልገውን እውቀትና ግንዛቤ በማግኘት ወደስራችሁ ስትመለሱ ተግባር ላይ በማዋል የሪከርድና ማህደር አደረጃጀቱን ዘመናዊ ማድረግ አለባቹ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

photo 2026 03 09 14 11 12


ስልጠናው ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃህፍት አገልግሎት በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች የሪከርድና ማህደር የሪከርድ ስራ አመራር ጽንሰ ሀሳብ፣ የሪከርድ አፈጣጠርና፣ አዘገጃጀትና አመዳደብ፣ የሪከርድ ዓይነቶችና ሌሎች ተያያዥ ርዕሶች ለቀጣይ ሶስት ቀናት እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀ ግብር ለመረዳት ተችሏል።