የ2025 የብሔራዊ አካውንት ስርዓት (SNA) እና የክፍያ ሚዛን (Balance of payment BMP7) ላይ ያተኮረ ወርክሾፕ መካሄድ ጀመረ

መጋቢት 22/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

7g9a5897

የ2025 የብሔራዊ አካውንት ስርዓት (SNA) እና የክፍያ ሚዛን (Balance of payment BMP7) ላይ ከአፍሪካ አባል ሀገራት ከተውጣጡ የስታቲስቲክስ ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የልማት ባንክና ዓለም አቀፍ ድርጅት ተወካዮች ጋር የውይይት መድረክ መካሄድ ጀመረ።

7g9a5854
7g9a5831

በወርክሾፑ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍስሀጽዩን የዚህ ዓይነት ወርክሾፕ በስታቲስቲክስ ዘርፍ ቅድሚያ መስጠት ያሉብንና ክፍተቶችን ለመለየት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚውን ለመለካት፣ አሁን ላይ ያለውን የስታቲስቲክስ ስርዓት ለማዘመን፣ በአህጉሪቱ የዕውቀት ሽግግርና እርሰ በዕርስ ለመማማር ያግዛል ሲሉ ገልፀዋል።

7g9a5839

የዓለም ኢኮኖሚ በከፍተኛ ለውጥ ውስጥ እያለፈ በመሆኑ ዲጂታላይዜሽን እሴት የሚፈጥርበትን፣ የሚለወጥበትና የሚከፋፈልበት መንገድ እየተቀየረ ነው ሲሉ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ ኃላፊ ሚስተር አዶም ጋጉሉም ገልፀዋል። በተጨማሪም ኃላፊው የ2025 የብሔራዊ አካውንት ስርዓትና የክፍያ ሚዛን አተገባበር ማሻሻያዎች የመለኪያ ማዕቀፎቻችን ወቅታዊ፣ ሁሉን አቀፍና ለታለመላቸው ዓላማ የሚመጥኑ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

a3a0142
a3a0033

የዚህ መድረክ ዓላማ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ለመማር፣ የመረጃ ክፍተትና የተቋማት ቅንጅትን ማነስ ያሉ ችግሮችን በጋራ ለመፍታትና የአፍሪካን ተጨባጭ ሁኔታ የሚመጥን የአተገባበር ፍኖተ ካርታ ለማዘጋጅት ነው ያሉት የስታቲስቲክስ ዲቪዝን ተጠባባቂ ዳይሬክተር ሻንታኑ ሙከርጄ ናቸው።

a3a0048
a3a0024

ወርክሾፑ በ2025 የብሔራዊ አካውንት ስርዓት (SNA) እና የክፍያ ሚዛን (Balance of payment BMP7) ላይ አዳዲስ የማክሮ ኢኮኖሚ የስታቲስቲክስ መመሪያዎችና ስትራቴጂዎችን በማዘጋጀት ለቀጣይ ሶስት ቀናት የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል።

a3a0129