የተወካዮች ምክር ቤት የስታቲስቲክስ አዋጅን አጸደቀ፡፡

ሰኔ 23/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የልማት ዕቅድን፣ የፖሊሲ ቀረፃንና ብሔራዊ ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራሞችን የመረጃ ፍላጎትን ለማሟላት እንዲያስችል የተዘጋጀው አዲሱ የስታቲስቲክስ አዋጅ ዛሬ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ፀድቋል፡፡

የፀደቀው የአዲሱ የስታቲስቲክስ አዋጅ በብሔራዊ የስታቲስቲክስ ስርዓት የባለድርሻ አካላትን ሚና እና ኃላፊነት የሚደነግግ፣ ሞያዊ ነፃነትን የሚያረጋግጥ፣ ተቋማዊ አቅምን የሚያጠናክር እንዲሁም ተስማሚ የሆኑ ደረጃዎች፣ ምደባዎችን፣ ሜታ ዳታዎችን እና የስታቲስቲክስ ስርዓቶችን በመጠቀም የሥራና የመረጃ ድግግሞሽ የሚያስቀር በአጠቃላይ በሀገር ደረጃ ወጥ የሆነ የስታቲስቲክስ መረጃ አቅርቦት እና የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖር የሚያስችል አዋጅ ነው፡፡

በአዋጁ የተካተቱት ሀገራዊ ግቦች እንዲሳኩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡

735563393 1415748653727264 3403107292816964140 n
733063063 2187182388681102 1740888274188056790 n
733415024 992804723547710 6498400431356228110 n
736182255 1881009895912848 582503176905800838 n
736420670 1567499868369059 3792692395184726845 n