የደቡብ ሱዳን ስታቲስቲክስ ቢሮ ዋና ዳይሬክተር ተቋሙን ጎበኙ

ሰኔ 25/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የደቡብ ሱዳን ስታቲስቲክስ ቢሮ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኡጉስቲኖ ቲንግ (Augustino Ting /Ph.D.) በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ ዳይሬክተሩ በተቋሙ የተሰሩ የሪፎርም ተግባራትን የጎበኙ ሲሆን ባደረጉት ጉብኘት ለተቋማቸው የሚሆኑ ልምድና ግንዛቤ እንዳገኙ ገልጾው ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋማቸው ለአፍሪካ እህት ተቋማት ያላቸውን ልምድና እውቀት ለማካፈል ዝግጁ መሆናቸውን አስረድተው፤ዋና ዳይሬክቴሩ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትን መርጠው በመጎበኝታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጻዋል።

a3a7231
a3a7419
a3a7365
a3a7251
a3a7429