በተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ላይ አተኩሮ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ

ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

ለኢትዮትጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤትና ለ26ቱ ቅ/ጽ/ቤቶች ሰራተኞች ዕምርታ በስታቲስቲክስ ልማት በሚል ርዕስ ከነሐሴ4_6/2018 ዓ.ም በተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ላይ አተኩሮ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

በስልጠናው መዝጊያ መርሀ ግብር ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ በስልጠናው ያገኘነውን ዕውቀትና ግንዛቤ እንዲሁም ባለፉት ሶስት አመታት ባከናወናቸው ታላላቅ ተግባራት የተገኙት የአመራር ጥበብ ልምድ ፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ፣ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና በቅንጅት መስራትና ሌሎች ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋትና ስኬቶቻችንን ይበልጥ በማላቅ በስታቲስቲክስ ዘርፍ በአህጉሪቱ መሪ ፤በአለም አቀፍ ስመ-ጥር፣ተወዳዳሪና የልህቀት ማዕከል የሆነ ተቋም ግንባታ እውን ለማድረግ የተጀመረውን ጉዞ ለማሳካት መላው የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች በከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነትና ትጋት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።

a3a1125
a3a1171
a3a0973
a3a0979
a3a0985
a3a0994
a3a1022
a3a1032 1
a3a1139